ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልፀዋል።

‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዲጂታላይዜሽንን በሚመለከት ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሸና ማብራሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል ብለዋል።

‎ይህ ትልቅ ቁጥር መሆኑን ጠቁመው 93 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ሲሆኑ 55 ሚሊዮን ዜጎች የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ሲሉም ገልጸዋል።

‎ይህ ኢትዮጵያን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የጀመረነው ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን አመላካች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top