The Building Management Office 

Building Management

VISION /ራዕይ/

“በ2025 ዓ.ም ደ/ታቦር ከተማን የብልፅግና ማዕከላት በማድረግ እና ተወዳዳሪ እና ምርታማ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ በመገንባት፣ በደ/ታቦር ከተማ የሚገነቡ ህንፃዎች የህንፃ ህጉን የጠበቁ፤ የህዝቡን ደህንነትና ጤንነት ያረጋገጡ እና የከተማውን ደረጃ የጠበቁ ሆነው ማየት”

MISSION /ተልዕኮ/

  • በከተማው የሚገነቡ ህንፃዎች የከተማዋን ደረጃ ጠብቀው የህብረተሰቡን ፍላጎት ያሟሉ የህዝብን ደህንነት እና ጤንነት ያረጋገጡ እንዲሆኑ መከታተል፣
  • በግልና በመንግሥት የሚገነቡ የህንፃ ግንባታዎች በተያዘላቸው ወጪ፣ ጊዜና ጥራት መሠረት ተጠናቀውና የመጠቀሚያ ፈቃድ አግኝተው ለህዝቡ ጥቅም እንዲውሉ ማድረግ፣
  • ሁሉም ፈፃሚ፣ አስፈፃሚ እና ማህበረሰቡ የህንፃ አዋጁን፣ ደንቡንና መመሪያውን አውቆ እንዲፈፅም ክትትል ማድርግ፣
  • የዘርፉን ተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላትን በማስተባበርና በማቀናጀት ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት፣

በህንፃ ግንባታ ፕሮጀክቶች ላይ ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለው ሥርዓት በመፍጠር እና የኮንስትራክሽን ተዋናዮችን አቅም በመገንባት ተወዳዳሪ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መገንባት፣

CORE VALUES / እሴቶች/

  1. ሀቀኝነት፣ ግልጸኝነት፣ ተጠያቂነት፤
  2. የአሠራር መርህን ተከትሎ መስራት፣
  3. ለውጤታማነትና ለሥራቅልጥፍና ዘወትር መትጋት፣
  4. ሁሌም በማያቋርጥ የመማርና የመማማር ሂደት ላይ መሆን፣
  5. ለህዝብ ጥቅም ቅድሚያ መስጠት እና ሁሉንም ሰው እኩል ማየትና
  6. የተለያዩ ሃሳቦችን በአግባቡ ማስተናገድ፤
  7. ወጪ ቆጣቢ አሠራርን መከተል፤
  8. የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባርን አጥብ ቆመታገል፤

Our location



Scroll to Top