የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ ዝግጁ መሆናቸውን የሰላምን አማራጭን የተቀበሉ ታጣቂዎች ተናገሩ፤

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በወገራ ወረዳ በእንቃሽ እና ቀንባዳ ቀበሌ አካባቢ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 25 ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበላቸው ተገለጸ።

‎የሰላም አማራጭን የተቀበሉ የታጣቂዎች እንደተናገሩት፦ የበደሉትን ሕዝብ ለመካስ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ጫካ ላይ ለሚገኙ ታጣቂዎች የሰላምን መንገድ መምረጥ አዋጪ መሆኑን መልዕክት ማስተላለፋቸውን ከወገራ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top