ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ ዲጂታል መርሃ ግብር ፈጠራ፣ ፍጥነትና እመርታን በማምጣት የማደግ ፍላጎታችንን ከአቅመችን ጋር እንዲናበብ እያደረገ ነው።
የዲጂታል 2025 ስትራቴጂ በኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በማስፋት ዘርፈ ብዙ ቱርፋቶች ተመዝግበውበታል።
በመንግስት አሰራር፣ በአገልግሎት አሰጣጥ እና በፋይናንስ ተደራሽነት ላይም ከፍተኛ ለውጥ መጥቷል።
ዛሬ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያስጀመርን ሲሆን፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች ዘላቂ የዲጂታል እመርታ እንዲመዘገብ ይሰራል።”
ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ብሔራዊ የዲጂታል ትራስፎርሜሽን ምክርቤት ሊቀመንብር

