ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔዎችን የሚያስሰው የጣና ፎረም 11ኛ ጉባኤውን ዛሬ በባሕር ዳር በማካሄድ በስኬት አጠናቋል።
ውብ ከተማ፣ ስልጡን ማኅበረሰብ እና ፍፁም ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ የጠበቃቸው አፍሪካውያን ምሑራን፣ ፖለቲከኞች፣ የሀገራት የቀድሞ መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ አምባሳደሮች፣ የአሕጉራዊ እና ዓለማቀፋዊ ድርጅቶች ተወካዮችም ቆይታቸው ያማረ እንደ ነበር ደስታ በተሞላበት ስሜት ገልጸዋል።
ጣና ፎረም በምስል

