መስከረም 5/2018 ዓ.ም) የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርእሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ “እምርታ እና ማንሰራራት” በሚል መሪቃል ውይይት እያደረጉ ነው።
የሕዳሴው ግድብ እውን መሆን ለኢትዮጵያውያን ያለውን ሁለንተናዊ ፋይዳ የሚዳስስ የውይይት መነሻ ጽሁፉ ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።
በውይይቱ መድረኩ የተቋሙ አመራሮች፣ የክቡር ርእሰ መስተዳድሩ አማካሪዎች እና ሰራተኞች ተሳታፊ ናቸው።