የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አረጋ ከበደ በደብረ ብርሃን ከተማ የብራውን ፉድስ የምግብ ማቀነባበሪያና ማምረቻ ፋብሪካ ሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

✅ሀገር የምትበለጽገው በእድልና በችሮታ ሳይኾን በጥረትና በታታሪ ትውልዶች አቅም ነው፡፡

✅ብራውን ፉድስ ፋብሪካ የመሥራትና የመቻል ብሎም የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የበለጸገ የምግብ ሥርዓት በማቅረብ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርግ ነው።

✅ፋብሪካው እንደ ክልል የኢኮኖሚ አቅም ከማጎልበት ባሻገር የፋብሪካዎች የግብዓት አቅርቦት ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባትን ያስቀረና እዚህ ተመርቶ እዚሁ ወደ ፋብሪካ የሚገባ ምርት መጠቀሙ ከፍተኛ ሚና አለው።

✅ሀገር በቀል ሰብሎችን በመጠቀም የተመጣጠነ የምግብ ሥርዓትን ለማሻሻል የሚሠራ ነው።

✅በተለይም የበቆሎ ምርትን ዋነኛ ግብዓት በማድረግ ልዩ ልዩ የበቆሎ ምግቦችን፣ የህጻናት ምግብ እና የበቆሎ ዱቄትን በማምረት የአመጋገብ ባሕልን የሚያሻሽል ነው፡፡

✅እንደ ሀገር ግዙፍ የኢኮኖሚ ምንጭ በሆነው የግብርና ምርት ላይ ያተኮረ መኾኑ ኢኮኖሚያዊ ትስስሩን የበለጠ የሚያጠናክር ነው።

✅የብራውን ፉድስ ፋብሪካ በግብርና ዘርፍ የሚመረቱ ግብዓቶችን የሚጠቀምና የበለጸገ የምግብ አቅርቦትን የሚያሳድግ ነው።

✅ፋብሪካው የክልሉ መንግስት የኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማሳደግ የያዘው የፖሊሲ አካል ነው።

✅ፍትሃዊ የሃብት ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንጻር ሰፊ አበርክቶ አለው።

✅እንደሀገር ያለውን የኢንዱስትሪ ፖሊሲ ትግበራን የሚደግፍና የክልሉን አጠቃላይ ልማት ለማሳደግ ሕዝቡ ከሚያደርገው ጥረት በተጨማሪ በሳል አመራር መስጠት ይገባል።

✅ፋብሪካው ከዕለት ቀለብ ፍጆታ በዘለለ ግብዓት የሚያመርቱ አርሶ አደሮችን የሚያፈራ እና የሥራ ባሕልን የሚቀይር ነው።

✅ለፋብሪካ ግብዓቶችን የሚያመርቱ አርሶ አደሮች ማፍራት እና የሥራ ባሕልን የሚቀይር ነው።

✅የአማራ ክልል እምቅ ሃብትና ሰፊ የሰው ኃይል ባለቤት በመሆኑ የግል ባለሃብቶችን በማስተሳሰር የሚፈለገውን የኢኮኖሚ ደረጃ ማምጣት ይቻላል።

✅የክልሉን ኢንዱስትሪ ልማት ለማጠናከርና ሰፊ የስራ እድል ፈጠራን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top